Search

የመንግሥትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ታጣቂ ኃይሎች በሰላም መግባታቸውን ቀጥለዋል

ማክሰኞ ታኅሣሥ 14, 2018 302

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን፣ መተማ ወረዳ እንዲሁም ማዕከላዊ ጎንደር ዞን፣ ጎንደር ዙሪያ ወረዳ የትጥቅ ትግልን አማራጭ አድርገው ሲቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ከነሙሉ ትጥቃቸው በሰላም ገብተዋል።

ታጣቂዎቹ ሲገቡ በዞን፣ወረዳ እና በመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው ከአማራ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

እስካሁን በዱር በገደሉ ያለአግባብ ስንገላታ ቆይተናል ያሉት ታጣቂዎቹ፤ ሌሎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎችም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲገቡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ለየአካባቢያቸው ዘላቂ ሰላምና ልማት የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸው፤ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የበደልነውን ህዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል ብለዋል።

#EBC #ebcdotstream #AmharaRegion #peace #disarmament