በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት እያስገነባ የሚገኘውን የኮንስትራክሽን ምህንድስናና ማኔጅመንት የልህቀት ማዕከልን የመስክ ምልከታ አካሂደዋል።
ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በሰንዳፋ ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ ያለው ይህ የልህቀት አካዳሚ ግንባታው ሲጠናቀቅ ኢንዱስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያስችላል ተብሏል።
በተለይም ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት፣ በኮንስትራክሽን ዘርፉ ላይ የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮችን በመምራት ዘርፉ ላይ ያሉ ችግሮችን መቅረፍ እንደሚያስችል ተገልጿል።
የኢኒስቲቲዩቱ ግንባታ በተጀመረ በ11 ወራት ውስጥም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ቋሚ ኮሚቴው አባላት ገልፀዋል።
ብሩክታዊት ተገኝ