Search

ትልቅ የዕውቀት ማዕከል ሆኖ እያገለገለ ያለው የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት

ቅዳሜ ታኅሣሥ 25, 2018 148

የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ትልቅ የዕውቀት ማዕከል ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ቤተ-መጻሕፍቱ አገልግሎት አሰጣጡን የሚያጎለብቱ የዲጂታል ሲስተሞችን አስጀምሯል።

በመድረኩም ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት የቦርድ ሰብሳቢ ቡዜና አልቃድር እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት፥ የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) ሃሳብ አመንጪነት ተገንብቶ ለአገልግሎት መብቃቱን አስታውሰዋል።

ቤተ-መጻሕፍቱ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ አንስቶ በመዲናዋ ትልቅ የዕውቀት ማዕከል ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በዕውቀትናክህሎት የተካነ ትውልድ በማፍራት ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ መሰረት የሚጥል መሆኑንም አብራርተዋል።

ቤተ-መጻሕፍቱ አገልግሎት አሰጣጡን በአዳዲስ አሰራሮች በማላቅ እና የንባብ ባህልን በማዳበር የዕውቀት ሽግግር ድልድይ በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ጥራ ያስጀመራቸው ዲጂታል ሥርዓቶችም የንባብ አገልግሎት አሰጣጥን በተሻለ አቅምና ጥራት ለማቅረብ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የዲጂታል አገልግሎቶቹም የቤተ-መጻሕፍቱን የተቀናጀ አስተዳደር በማሳለጥተመራማሪዎች የጥናትና ምርምር ሥራዎቻቸውን ካሉበት ቦታ ሆነው በቀላሉማከናወን የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።

በቀጣይም ነዋሪዎች የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት 24 ሰዓት አገልግሎት የፈጠረውን ምቹ የንባብ ምኅዳር ሊጠቀሙበት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

#EBC #ebcdotstream #AbrehotLibrary