መንግሥት የዘረጋውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ ደቡብ ጎንደር ዞን ባሉ ወረዳዎች በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የታጠቁ ቡድኖች የሰላም አማራጭን ተቀብለው ገብተዋል።
በአቀባበሉ ላይ የተገኙት የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ጥላሁን ደጀኔ፥ አሁንም በጫካ ያሉ ታጣቂዎች የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ ሰላምን መርጠው መግባት አለባቸው ብለዋል።
በደቡብ ጎንደር ዞን የሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች ሰላምን ከሚያውኩ አካላት ነጻ እንዲሆኑ የክልል እና የፌዴራል የጸጥታ አካላት ትልቅ ሥራ ሲያከናውኑ እንደነበርም መግለፃቸውን የአማራ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
በቀጣይም የሕዝብ ግንኙነት ሥራዎቻችን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምን የመገንባት ሂደቱ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
#EBCDotstream #SouthGondar #Peace