Search

ባህር ዳር ከተማ ክለብ ላይሰንሲንግን ያሟላ ብቸኛ ክለብ ሆኗል

ክለቦች በካፍ ክለብ ላይሰንሲንግ ኦንላይን ፕላትፎርም (CLOP) ላይ ሲመዘገቡ ያቀረቧቸውን ሰነዶች መሠረት በማድረግ ያሉበትን ደረጃ አውቀዋል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኳስ ፌደሬሽን የክለብ ላይሰንሲንግ የፍትህ አካልን መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ያሉበትን ደረጃ ይፋ አድርጓል።

2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከሚሳተፉት 20 ክለቦች ሁሉንም መስፈርቶች ካለ ማስጠንቀቂያ ማሟላት የቻለው ብቸኛ ክለብ ባህር ዳር ከተማ ሀኗል።

ቀሪ 19 ክለቦች ያላሟሏቸውን ጉዳዮች እንዲያሟሉ የጊዜ ገደብም ተቀምጦላቸዋል።

በውሳኔዎች ላይ ቅሬታ አቅራቢ ክለብ ይግባኝ የመጠየቅ መብቱ የተጠበቀ እንደሆነ ፌደሬሽኑ አሳውቋል።

በአንተነህ ሲሳይ