Search

በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀመረ

ሓሙስ ሰኔ 11, 2018 28

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰኔ 11 እና ሰኔ 12/2018 ዓ.ም የሚሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ201 የፈተና ጣቢያዎች በዛሬው ዕለት መሰጠት ተጀምሯል።

የከተማ አቀፍ ፈተናውን አጀማመር ለመመልከት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች በዳግማዊ ብርሃን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን ተመልክተዋል።

May be an image of one or more people, people studying and text

በከተማ አስተዳደሩ በአጠቃላይ 86 ሺህ 783 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበው ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል።

May be an image of one or more people and people studying

ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ ቀደም ብሎ ኮማንድ ፖስት ከማደራጀት ጀምሮ ልምድ ያላቸው አስፈጻሚዎች፣ አመራሮችና የጸጥታ አካላት በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች መመደባቸውን አስታውቀዋል።

ተማሪዎች ውጤታማ ይሆኑ ዘንድ በትምህርት ቤቶች ውስጥ የማጠናከሪያ ትምህርቶች ከመሰጠታቸው ባሻገር ደረጃውን የጠበቀ የሞዴል ፈተና እንዲወስዱ የተደረገ ሲሆን ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ከኩረጃ ነፃ እንዲሆን ለተማሪዎችና ለፈተና አስፈጻሚዎች ቅድመ ገለጻ (ኦሬንቴሽን) ተሰጥቷል።

በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ላለፉት ሦስት ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ በስኬት መጠናቀቁ ይታወቃል።