Search

የአዲስ አበባ ከተማ የ2019 በጀት 502 ነጥብ 27 ቢሊየን ብር ሆኖ ፀደቀ

ሰኞ ሐምሌ 06, 2018 50

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማ አስተዳር ምክር ቤት ባካሄደው 3 ዙር 5 ዓመት የሥራ ዘመን 4 መደበኛ ጉባዔ በሁለተኛ ቀን ውሎው በከተማዋ 2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ በመወያየት፣ የአስተዳደሩን አጠቃላይ በጀት 502 ነጥብ 27 ቢሊየን ብር እንዲሆን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡

የፀደቀው በጀት ከባለፈው 2018 . ተመሳሳይ በጀት ጋር ሲነጻፀር 152 ነጥብ 26 ቢሊዮን ብር ወይም 43 ነጥብ 5 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተገልጿል፡፡

ከፀደቀው በጀት ውስጥ 359 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ለካፒታል፣ 142 ነጥብ 97 ቢሊየን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 16 ቢሊየን ብር የመጠባበቂያ በጀት መሆኑ ተመላክቷል።

በጀቱ የከተማ አስተዳደሩን 10 እና 5 ዓመት የልማት ስትራቴጂዎች ግቦችንና እና የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማሳካት ያለመ ነው መባሉን የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል።

የኢኮኖሚ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል፣ የሥራ እድል፣ ፈጠራ፣ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ማጠናከር፣ የመሠረተ-ልማት ግንባታና ጥገና በዘላቂነት ማረጋገጥ፣ የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ኮሪደር ልማትን ጨምሮ መጠበቅና ለማስቀጠል የሚውል እንደሆነም ተገልጿል።

እንዲሁም የትራንስፖርትና የትራፊክ ፍሰትን ማሻሻል፣ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ብልሹ አሠራርንና ሌብነትን ማስቀረት፣ የሰው ሃብት ልማት የማስፈፀም አቅምን መገንባት፣ ሰላምና ፀጥታ ማረጋገጥ፣ የቤት ልማት ማጠናከር የውሃ አቅርቦት እና ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶች በተሟላ ለማጠናቀቅ እና የመንገድ መሰረተ ልማት ለማስፋፋት የሚውል መሆኑ በቀረበው የበጀት ማብራሪያ ተመላክቷል።

 

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: