ኢትዮ ቴሌኮም አና የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በባሕርዳር ከተማ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ፣ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ግብርን በቴሌ ብር እንዲሰበስብ የሚያስችለው ነው።
ስምምነቱ ዜጎች ያለምንም ድካም እና እንግልት ባሉበት ቦታ ሆነው በቴሌ ብር አማካኝነት ግብራቸውን በቀላሉ እንዲከፍሉ የሚያስችል ስለመሆኑ የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አዳነ ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ስምምነቱ የተቋሙን የገቢ አሰባሰብ ሂደት በማዘመን እና ብልሹ አሠራሮችን በማስቀረት ቀልጣፋ እና ፍትሐዊ የገቢ አሰባሰብን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።
ቀደም ብሎ ከባሕርዳር ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በክልሉ የተተገበረውን ኤሌክትሮኒክ የታክስ አሥተዳደር ሥርዓት (ኢ-ታክስ ሲስተም) በመጠቀም በ2018 በጀት ዓመት 90 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን ቢሮ ኃላፊው ጠቅሰዋል።
ቴሌ ብር ወደ ሥራ ከገባ ጊዜ ጀምሮ በመተግበሪያው 9 ትሪሊዮን ብር የሚጠጋ የገንዘብ ዝውውር ስለመፈፀሙ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል። ከ60 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራትም ተችሏል።
በተስፋሁን ደስታ
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: