በጉባኤው ላይ የ6ኛ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤን በማፅደቅ የጀመረ ሲሆን ምክር ቤቱ በቆይታው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ አያን አብዲ ተናግረዋል።
የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርትን ማዳመጥ እና ማፅደቅ፣ የክልሉ ምክር ቤት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርትን ማዳመጥ እና ማፅደቅ፣ የፍርድ ቤት እና ዋና ኦዲተር ሪፖርቶችን ማዳመጥ እና ማፅደቅ ከተቀመጡ አጀንዳዎች መካከል ተጠቃሾቹ ናቸው።
ምክር ቤቱ በመጨረሻም የክልሉን የ2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀትን እንዲሁም የተለያዩ ሹመቶችን በማፅደቅ ጉባኤውን እንደሚያጠናቅቅ የወጣው መርሐ ግብር ያሳያል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: