Search

የሶማሌ ክልል ምክር ቤት የ6ኛ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

ሰኞ ሐምሌ 20, 2018 30

በጉባኤው ላይ 6 ዘመን 10 መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤን በማፅደቅ የጀመረ ሲሆን ምክር ቤቱ በቆይታው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ አያን አብዲ ተናግረዋል።

የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት 2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርትን ማዳመጥ እና ማፅደቅ፣ የክልሉ ምክር ቤት /ቤት 2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርትን ማዳመጥ እና ማፅደቅ፣ የፍርድ ቤት እና ዋና ኦዲተር ሪፖርቶችን ማዳመጥ እና ማፅደቅ ከተቀመጡ አጀንዳዎች መካከል ተጠቃሾቹ ናቸው።

ምክር ቤቱ በመጨረሻም የክልሉን 2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀትን እንዲሁም የተለያዩ ሹመቶችን በማፅደቅ ጉባኤውን እንደሚያጠናቅቅ የወጣው መርሐ ግብር ያሳያል።

በቴዎድሮስ ታደሰ

 

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: