Search

በቀድሞ የሲዳማ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ላይ የጽኑ እስራት እና የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ ተላለፈ

ሰኞ ሐምሌ 20, 2018 86

የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀድሞ የሲዳማ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ እና በቀድሞው የፖሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ ላይ የጽኑ እስራት እና የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ።

የክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በሰው እና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ ለክልሉ ፍትህ ቢሮ ያቀረበውን የምርመራ መዝገብ የተመለከተው ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ሥልጣንን አላግባብ በመገልገል "የሲዳማ ነፃነት ሠራዊት" የተባለ ታጣቂ ቡድን በማደራጀት ተደራራቢ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን በማረጋገጥ ጥፋተኛ ብሏቸዋል።

በዚህም መሠረት ፍርድ ቤቱ ሐምሌ 20 ቀን 2018 . በዋለው ችሎት አንደኛ ተከሳሽ አቶ ዓለማየሁ ጢሞቲዎስ 10 ዓመት 5 ወር ጽኑ እስራት እና 4 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ ወስኗል።

ሁለተኛ ተከሳሽ አቶ ሽመልስ ቶማስ ደግሞ 1 ዓመት 6 ወር ጽኑ እስራት እና 1 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ ውሳኔ ማስተላለፉን ከፌዴራል ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: