Search

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2019 በጀት 67 ቢሊየን ብር ሆኖ ፀደቀ

ዓርብ ነሐሴ 01, 2018 133

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

ምክር ቤቱ የክልሉን የ2019 አጠቃላይ ረቂቅ በጀት ላይ ውይይት በማድረግ በጀቱ 67 ቢሊየን ብር እንዲሆን በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል።

ከጠቅላላው በጀት ውስጥ 47 በመቶው በመንግሥት ግምጃ ቤት የሚሸፈን ሲሆን፣ 53 በመቶው ደግሞ ከክልሉ የውስጥ ገቢ እንደሚሸፈን ተገልጿል።

የ2019 በጀት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ30.3 ቢሊየን ብር ጭማሪ እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፣ በምክር ቤቱ በ2018 በጀት ዓመት ሪፖርት እና የ2019 ጠቋሚ እቅድ ላይ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

በቶማስ ኃይሉ

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: