የአፋር ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባዔውን ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል።
ምክር ቤቱ ለሚቀጥሉት ሶስት ቀናት በሚያካሂደው በዚህ ጉባዔ፤ በክልሉ አስፈጻሚ አካላት፣ በጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የቀረቡትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቶች ላይ ሰፊ ውይይት የሚያደርግ ይሆናል።
በጉባዔው መክፈቻ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በሪፖርታቸው ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የተከናወኑ ተግባራትን፣ ከአጎራባች ክልሎች ጋር ህዝባዊ ውይይቶችን በማድረግ ረገድ የተገኘውን ሰላምና መልካም ግንኙነት እንዲሁም በአጠቃላይ በክልሉ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና በሰላም ዙሪያ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል፣ የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማል ጉባዔውን ሲያስጀምሩ ባደረጉት ንግግር፣ ምክር ቤቱ በህዝብ የተሰጠውን አደራ በመወጣት የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራትን በየደረጃው ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።
በአሊ አህመድ
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: