Search

13ኛው የምሥራቅ አፍሪካ ጤና ክብካቤ ፌዴሬሽን ጉባኤ እና ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

ማክሰኞ ነሐሴ 12, 2018 146

የጤና ሚኒስቴር ከነሐሴ 15 እስከ 17 ቀን 2018 . የሚካሄደውን 13ኛውን የምሥራቅ አፍሪካ ጤና ክብካቤ ፌዴሬሽን ጉባኤ እና ዓለም አቀፍ የጤና ኤግዚቢሽን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የምሥራቅ አፍሪካን የጤና ኢኮኖሚ መገንባትበሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ በምሥራቅ አፍሪካ በጤናው ዘርፍ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት እና ጤናን ለሀገር ሉዓላዊነት እንዲሁም ለኢኮኖሚ የጀርባ አጥንትነት ለማድረግ ያለመ ነው።

በጉባኤው ላይ 20 በላይ ሀገራት የተውጣጡ 2 ሺህ መሪዎች፣ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት፣ ከእስያ እና ከመላው ዓለም የሚመጡ 30 በላይ ታዋቂ የሕክምና አምራች ድርጅቶች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ባለሀብቶች እና የፈጠራ ባለሙያዎች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ / ፍሬሕወት አበበ እንዳብራሩት ጉባኤው በኢትዮጵያ የጤናውን ዘርፍ ኢኮኖሚ ለማጠናከር፣ መድኃኒቶችን እና የሕክምና ቁሳቁሶችን በሀገር ውስጥና በቀጠናው በማምረት ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም እንደ ሀገር አህጉራዊ ትስስርን በማጠናከር በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕቀፍ ውስጥ የጤና የንግድ ሰንሰለቶችን በመፍጠር በጋራ ለመሥራት እንደሚያስችል ገልጸዋል።

በኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር በምሥራቅ አፍሪካ ጤና ክብካቤ ፌዴሬሽን እና በኢትዮጵያ ጤና ክብካቤ ፌዴሬሽን ትብብር የተዘጋጀው 13ኛው የምሥራቅ አፍሪካ ጤና ክብካቤ ፌዴሬሽን ጉባኤ እና ዓለም አቀፍ የጤና ኤግዚቢሽን በአድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል።

በሰናይት ሠይፉ

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: