Search

216ኛው የለንደን ደርቢ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቀቀ

እሑድ ጳጉሜን 01, 2018 166

በሦስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በኢሚሬትስ ቼልሲን ያስተናገደው አርሰናል 2 1 በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።

አዲስ ፈራሚው ሞርጋን ሮጀርስ ጨዋታው በተጀመረ 2ኛው ደቂቃ ባሰቆጠራት ግብ ቼልሲን ቀዳሚ ቢያደርግም፣ 25ኛው ደቂቃ ላይ ካይ ሃቨርትዝ የአርሰናልን የአቻነት ግብ አስቆጥሮ የመጀመሪያው አጋማሽ 1 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።

ሆኖም በሁለተኛው አጋማሽ 50ኛው ደቂቃ ላይ ማርቲን ኦዲጋርድ ያስቆጠራት ግብ አርሰናልን አሸናፊ አድርጋለች።

ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በሦስት ተከታታይ ድሉ 9 ነጥብ ከሲቲ በግብ መጠን ተበልጦ ሁለተኛ ላይ ተቀምጧል። ቼልሲ በአንፃሩ 6 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

አርሰናል 4ኛው ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ቀጣይ ቅዳሜ ወደ ስታዲየም ኦፍ ላይት አቅንቶ ሰንደርላንድን ሲገጥም፣ ቼልሲ በተመሳሳይ ቅዳሜ ቀን በስታምፎርድ ብሪጅ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ አዲስ አዳጊውን ሃል ሲቲን ያስተናግዳል።

 

 

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: