በአፋር ክልል በመካከለኛው እና በታችኛው አዋሽ የጎርፍ አደጋ ስጋትን ለመቀነስ እየተሠራ መሆኑን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአዋሽ ቤዚን አስተዳደር ጽ/ቤት ገለፀ።
በነዚህ አካባቢዎች ሰሞኑን የጣለው ዝናብ መጠኑ ከፍተኛ እንደነበር የገለፁት የጽ/ቤቱ ሀላፊ ኢንጂነር አደን አብዶ፤ በኃይለኛ የውሃ ፍሰት ፈርሰው የነበሩ የጎርፍ መከላከያዎችን ከየአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን መልሶ መጠገን መቻሉን ለኢቲቪ ተናግረዋል።
የአዋሽ ውሃ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ከጎርፍ መከላከል ግብረ ኃይል ጋር በመሆን ህብረተሰቡን ወደ ከፍተኛ ቦታዎች የማዛወር እንዲሁም በግብርና ሥራ ላይ ጉዳት እንዳያስከትል የመከላከል ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም ከክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በየአካባቢው በተመደቡ ባለሙያዎች አማካይነት ለህብረተሰቡ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክት የመስጠት ሥራዎች እየተከናወነ መሆኑን ኢንጂነር አደን ገልፀዋል።
በሁሴን መሐመድ
#ኢቢሲዶትስትሪም #ኢቲቪ #አፋር #አዋሽ #ጎርፍ