Search

በ10 ቀናት ውስጥ የተሠራው የጌደብ ወንዝ ድልድይ

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017 120

በቅርቡ በጎርፍ የፈረሰው የጌደብ ወንዝ ድልድይ በ10 ቀናት ውስጥ በምስሉ ላይ በሚታየው መሰረት በተገጣጣሚ ብረት ተሠርቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል።

በደብረ ማርቆስ ባህር ባሕር ዳር መስመር አማኑኤል ከተማ የሚገኘው የጌደብ ወንዝ ድልድይ ነሐሴ 3/2017 ሌሊትጮቄ ተራራ ዙሪያ የጣለው ከባድ ዝናብ በፈጠረው ጎርፍ ፈርሶ እንደነበር ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ ድልድዩ በ10 ቀናት ውስጥ በተገጣጣሚ ብረት በፍጥነት ተሠርቶ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል።

በአንድ ጊዜ አንድ መኪና የማስተናገድ አቅም ያለው አዲሱ የብረት ድልድይ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል ተብሏል።

በራሄል ፍሬው

#ኢቢሲዶትስትሪም #ኢቲቪ #ምስራቅጎጃም #ጌደብድልድይ