Search

የትምህርት አገልግሎትን ከገንዘብ ጋር ብቻ መያያዝ ሀገር የሚጎዳ ነው - የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ሰኞ ነሐሴ 19, 2017 49

የትምህርትን  አገልግሎትን ከገንዘብ ጋር ብቻ መያያዝ ሀገርን እንደሚጎዳ  የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ  ተናገሩ።

በኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዳግም ምዝገባ  አስፈላጊነትን በተመለከ በትምህርት ሚኒስቴር በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። 

የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከሀገር ፍላጎት ጋር በማጣጣም በዓለም ነባራዊ ሁኔታ በመቃኘት መገንባት እንደሚገባም ነው የትምህርት ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት የተናገሩት

የትምህርት ተቋማት ለሀገር ግንባታ ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ እና ወደፊት እንዴት መሄድ እንደለባቸው መግባባት ያሻል ብለዋል። 

በኢትዮጵያ በትምህርት ሥርዓቱ ያለውን ችግር ለማጥራት ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም፤ ጉዳዩን በታሰበው ፍጥነት መፍታት አለመቻሉንም ጠቁመዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያዘጋጀው የዳግም ምዝገባ፤ ተቋማት የተፈቀደውን የተማሪ  እንየዲያስተምሩ፣ በራሳቸው ህንፃ ወይም ሙሉ ህንፃ ተካራይተው በምቹ  ሁኔታ እንዲያስተምሩ፣ ተቋማት ሰነዶቻቸውን በአዲሱ መመሪያ መሰረት እንዲከዉኑ፣ የአሰራር ሥርዓቶችንና መዋቅሮችን እንዲከልሱ፣ የመምህራን ቅጥርን እንዲያሟሉ እንዲሁም ለማህበረሰብን ጠቃሚ ጥናትና ምርምር እንዲሰሩ ያስችላል ተብሏል።

ዳግም ምዝገባው በተቋማቱ የሕዝብ እምነት ለመገንባት ግልፅነትተጠያቂነት ለማስፈን ብሎም የጠራ ሙሉ መረጃ እንዲኖራቸው ለማድረግ  እንደሚያግዝ ተገልጿል።

በላፉት ወራት በግል ተቋሟት ሲካሄድ የቆየው ጥናት ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበትም ይገኛል።

በላሉ ኢታላ