በ4ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሜዳው ከኖቲንግሀም ፎረስት የተጫወተው አርሰናል 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በኢምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ማርቲን ዙቢሜንዲ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ቪክቶር ዮኬሬስ አንድ ግብ አስቆጥሯል፡፡
በ3ኛ ሳምንት በሊቨርፑል የተሸነፉት መድፈኞቹ ወደ አሸናፊነት የተመለሱበትን ወሳኝ ድል አስመዝግበዋል፡፡
ዊሊያም ሳሊባ እና ቡካዮ ሳካን በጉዳት ያጣው አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ አምስቱንም አዲስ ፈራሚዎች በቋሚነት በተጠቀመበት ጨዋታ ከ4 የሊግ ጨዋታዎች ሦስተኛ ድሉን አስመዝግቧል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ