የቀድሞው የባርሴሎና ተከላካይ ሳሙኤል ኡምቲቲ ጫማውን መስቀሉን ይፋ አድርጓል፡፡
በካታላኑ ክለብ 7 ዓመታትን ያሳለፈው ፈረንሳዊው ከክለቡ ጋር ሁለት የላሊጋ እና ሦስት የከፓ ደልሬ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡
ኡምቲቲ በተደጋጋሚ ባጋጠመው የጉልበት ጉዳት ምክንያት ገና በ31 ዓመቱ እግር ኳስ ለማቆም መገደዱን አሳውቋል፡፡
ተከላካዩ ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጋር የ2018ቱን ዓለም ዋንጫ ማሳካቱም ይታወሳል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ