Search

የከንቲባ አዳነች አቤቤ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

ዓርብ መስከረም 16, 2018 39

እንኳን ለደመራ እና መስቀል በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ።
የከተማችን ልዩ ድምቀት ለሆነው እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የመስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ነው።
ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እንኳን በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ፤ በዓሉ የአብሮነት፣ የፍቅር እና የሰላም እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። መልካም በዓል!
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ