Search

ፖለቲካዊ ነፃነት ያለ ኢኮኖሚ ኃይል በቂ አይደለም፦ ጆን ድራማኒ ማሃማ

ሓሙስ ኅዳር 11, 2018 166

የጋናው ፕሬዚዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ለአፍሪካ እውነተኛ ነፃነት የፖለቲካ ነፃነት ብቻውን በቂ እንዳልሆነ ገለጹ።

ፕሬዚዳንቱ በአፍሪካ ግስጋሴ ላይ ገደብ የሆኑ አዳዲስ እና ውስብስብ ኃይሎች ያሏቸውን ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊና ርዕዮተ-ዓለማዊ ጉዳዮች መጋፈጥ የግድ መሆኑን አሳስበዋል።

በ‘ፓን አፍሪካን ፕሮግሬሲቭ ፍሮንት’ ጉባዔ ላይ የተገኙት ፕሬዚዳንት ማሃማ፥ ቅኝ ገዥነትን በማስወገድ የተገኙት ታሪካዊ ድሎች ራስን በራስ የማስተዳደርን በር ቢከፍቱም፤ "እውነተኛ ነፃነት ግን ከዚህ የበለጠ ብዙ ሥራ ይጠይቃል" ብለዋል።

አፍሪካ በሐብቷ የበለፀገች ሆናም በዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ድሃ መሆኗን የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፤ አዲሱ የፓን አፍሪካን ትግል የኢኮኖሚ ለውጥ፣ ቴክኖሎጂያዊ ሉዓላዊነት፣ የአየር ንብረት ፍትሕ እና ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓትን ለማረጋገጥ መሆን አለበት ነው ያሉት።

በአህጉር አቀፍ ውህደት ዙሪያ ብዙ ንግግር ቢደረግም፣ በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ ገና 20 በመቶ በታች ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱዕ ይህን ማስተካከል እንደሚገባ አሳስበዋል።

የዛሬው ትግልቅኝ ግዛትነትን ከመዋጋት ትግል ይልቅ ውስብስብ እና ፈታኝ ነውበማለት ትግሉን በድል መወጣት ለአፍሪካ ክብር እና ብልፅግና ወሳኝ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

በሰለሞን ገዳ

#ebcdotstream #panafricanism #ppf #Mahama