Search

ከ23 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ማዳን የተቻለበት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት

ማክሰኞ ነሐሴ 06, 2017 126

በመንግስትና በማኅበረሰቡ ያልተሸፈኑ የልማት ሥራዎችንና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማከናወን፤ 23.3 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማዳን እንደተቻለ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታውቋል።

ይህ የተባለው እየተካሄደ በሚገኘው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች ሴክተር አራተኛ ጉባዔ ላይ ነው።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በክረምትና የበጋ ወራት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 25ሚሊዮን በላይ ወጣቶች ተሳትፎ ማድረጋቸውንም ነው የገለጸው።

በዚሁ ወቅት 2017 በጀት ዓመት ሪፖርትን ያቀረቡት  የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ማዕረግ መኮንን፥  በክረምት እና የበጋ ወራት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሐ-ግብሮች "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል መካሄዱን ጠቅሰዋል።

በተለያዩ የስምሪት መስኮች 25.9 ሚሊየን በላይ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መሳተፍ ችለዋልም ነው ያሉት።

59.1 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የሕበረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለም አንስተዋል።

የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (/) ለዜጎች የላቀ ክብር በትጋት እንሰራለን ያሉ ሲሆን፤ በተለይም ተቋሙ የጀመረውን የማኅበራዊ ጥበቃ ሥርዓት ዝርጋታን በማጠናከር ዜጎችን በልማት ተሳታፊ ለማድረግ ትኩረት እንደሚደረግ ገልጸዋል።

 

በአዲሱ ገረመው