Search

1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል የፊታችን ረቡዕ ይከበራል

ሓሙስ ግንቦት 13, 2018 41

የ1447ኛው . (2018 .ል) የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል የፊታችን ረቡዕ እንደሚከበር የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አስታወቀ።

ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤቱ በዓሉን አስመልክቶ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ለኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ የእምነቱ ተከታዮችእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ በመግለጫው፣ ዋናው የሐጅ ቀን (ውቅፍ ዓረፋ) ማክሰኞ ዙል ሒጃ 9 ቀን መሆኑን ጠቅሶ፣ ዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) ረቡዕ ዙል ሒጃ 10 (ግንቦት 19) ቀን ተከብሮ እንደሚውል አስታውቋል።

በዓሉ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን የገለጸው ፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት፣ ምዕመናን በዓሉን ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን በመርዳት እንዲያከብሩት ጠይቋል።

#world #Ethiopia #Islam #Muslims #Eid #EidAlAdha #EBC