Search

ግምታቸው ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ የሆኑ ሕገ ወጥ መድኃኒቶች ተወገዱ

ሓሙስ ነሐሴ 08, 2017 132

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ግምታቸው 1 ቢሊዮን ብር በላይ የሆኑ ሕገ ወጥ መድኃኒቶች እንዲወገዱ ማድረጉን አስታወቀ

ሕገ ወጥ መድኃኒቶቹ በዋናነት የባለስልጣን መስርያ ቤቱን መስፈርት የማያሟሉ ናቸው የተባለ ሲሆን፤ ለአብነትም የወባን ጨምሮ የሌሎች ህመሞች ያልተመዘገቡ መድኃኒቶች ጥራትደህንነትና ፈዋሽነታቸው የማይታወቅ፣ በኮንትሮባንድ የገቡና ሕጋዊ ደረሰኝ የሌላቸው መድኃኒቶች እንደሆኑ ተገልፅዋል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ በሰጡት መግለጫ መስሪያ ቤቱ 2017 በጀት ዓመት በርካታ የቁጥጥር ተግባራትን እንዳከናወነ አስረድተዋል።

ተቋሙ የሕብረተሰብ ጤናን ለመጠበቅ በምግብመድኃኒትበህክምና መሳሪያዎችበውበት መጠበቅያና በትምባሆ ዙሪያ ከክልሎች ጋር በመሆን ባካሄደው ቁጥጥር አበረታች ውጤት ማስመዝገቡ ተገልፅዋል።

ከምግብ ጋር በተያያዘ በአምራቾችና አስመጪዎችና አከፋፋዮች ላይ  በአጠቃላይ 285 የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ፣ 384 የፍቃድ ስረዛ፣ 39 የእሸጋና 310 የእገዳ እርምጃ ተወሰዷልም ነው ያሉት

ከመድኃኒት ጋር በተያያዘም ግምታቸው 1 ቢሊዮን ብር በላይ የሆኑ መድሃኒቶች በሕብረተሰብ ጤና ላይ ችግር ከማድረሳቸው በፊት ከክልሎች ጋር በመተባበር እንዲወገዱ መደረጉን ዋና ዳይሬክተሯ ሄራን ገርባ አስታውቀዋል።

በመሀመድ ራህመቶ