Search

የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት ያሰሩት ቃልኪዳን - የአዋዛ ስምምነት ምንድነው?

ዓርብ ነሐሴ 09, 2017 155

ከባህር  በር አማራጭ መራቅ የሚያስከትላቸውን ችግሮች ለመፍታት በማሰብ ነበር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባህር በር የሌላቸው ታዳጊ ሀገራትን ጉባዔ ማካሄድ የጀመረው፡፡

.. 2003 ለመጀመሪያ ጊዜ በካዛኪስታን አልማቲ ከተማ የተካሄደው ጉባዔየሀገራቱ የባህር ላይ ትራንስፖት እንዲመቻች  እና የመተላለፊያ ኮሪደር እንዲያገኙ ብሎም ለባህር በር ተመጣጣኝ የሆነ ክፍያ እንዲከፍሉ በሚያስችላቸው ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር፡፡

ይህንንም እንዲያጠናክር እን በአስተናጋጅ ከተማዋ የተሰየመው  የአልማቲ ዲክላሬሽንየተፈረመው፡፡

የስምምነቱ ነጥቦች .. 2003 እስከ 2013 ተግባራዊ እንዲሆን የተሰራም ነበር፡፡

በኋላም በሁለተኛው ጉባዔ ቪየና ተካሄደ ። በቪየና ስምምነት መሰረትም ሀገራትን እንዴት ማሳደግ እንደሚቻል በተለይም የንግድ ትስስራቸው እንዲጨምር ማድረግላይ ያተኮረ አጀንዳ ተነስቷል።

ጥሬ እቃ ከመላክ በውስጥ አቅም ማምረት እንዲቻል የድንበር ተሻጋሪ ንግድ እክሎችን መቅረፍ ብሎም ለችግሮች ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅምን ማጠናከር ላይ እንዲሰራም አቅጣጫ ያስቀመጠ ነበርል፡፡

የቪየና ስምምነትበዚህ መልኩ ተወልዶ .. 2014-2024 እንዲተገበር የተወሰነ እንደነበር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡

ቱርኪሚስታን ያስተናገደችው 3ተኛው የባህር በር የሌላቸው ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ ደግም ሀገራቱ የባህር በር አማራጭ ስለሌላቸው የጂኦግራፊ እስረኛ መሆን እንደሌለባቸው ያነሳ ሆኖ አልፏል፡፡

ይህን ሀሳብ የሚያጠናክረውየአዋዛ ዲክላሬሽንበተሳታፊ ሀገራት ተስፋ የተጣለበት መሆኑንም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (/) ገልጸዋል።

.. 2024 ሃሳቡ ተጠንስሶ 3ተኛው የተመድ ጉባዔ ላይ ተግባራዊነቱ የተመከረበትየአዋዛ ዲክላሬሽንየሀገራቱ ተስፋ መሆኑን ምክትል ሰብሳቢው ይገልፃሉ::

የሳይንስና ቴክኖሎጂና ፈጠራን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ምርታማነት መጨመር ብሎም ለገቢ ምርት የሚወጣውን የማጓጓዣ ወጪ መቀነስ አንዱ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የተፋጠነ የንግድ ትስስር እንዲፈጠር  እና በሌሎች ሀገራት ፈቃድ ላይ እንዳይመሰረት ማድረግ በተለይም ይህ እንዲሆን የሚያስችል የመሰረተ ልማት ትስስር መፍጠር ላይ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡

ከዚህ ባሻገር የፋይናንስ እና የቴክኒክ አተገባበር እገዛ ያለው መሆኑን በጉባዔው ተሳታፊ የነበሩት / ፈቲህ ለኢቲቪ ተናግረዋል፡፡

ጂኦግራፊ የሀገራትን እጣ ፋንታ ሊወስን አይገባምበሚል ስምምነት ጉባዔው መጠናቀቁንም ነው የገለፁት፡፡

 

በአፎሚያ ክበበው