Search

የኤችአይቪ (ኤድስ) እና የቲቢ ምርመራና ሕክምና አገልግሎትን የማጠናከር ሥራ

ቅዳሜ ነሐሴ 10, 2017 198

የኤችአይቪ (ኤድስ) እና የቲቢ ምርመራ እና ሕክምና አገልግሎት መሻሻል ማሳየቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል።

ከክልሉ ሁሉም ዞኖች የተውጣጡ  የጤና ባለሙያዎች የተቀናጀ የቲቢ እና የኤችአይቪ (ኤድስ) ምርመራ እናክምናን ለማጎልበት የሚያስችል ምክክር በታርጫ ከተማ አካሂደዋል።

በዚሁ ወቅት የቢሮው ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንዳሉት፥ በክልሉሁሉም አካባቢዎች አገልግሎቱን ለማጠናከር እና ለማስፋት በማህበረሰብ አቀፍ ፕሮግራም የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።

በዚህም በክልሉ በሚገኙ 44 የጤና ተቋማት አገልሎቱን ይበልጥ ለማጎልበት መቻሉን አቶ ኢብራሂም ጠቁመዋል።

ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች እና የሥራ ቦታዎች የጤና ተቋማትን የመገንባትና በዘመናዊ የሕክምና ግብዓቶች የማደራጀት ሥራም እየተከናወነ እንደሚገኝ  አብራርተዋል።

በክልሉ 200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የኤችአይቪ (ኤድስ) ምርመራ ተደራሽ ማድረግ መቻሉ እና ቫይረሱ በደማቸው የተገኘባቸው 9 ሺህ 38 ዜጎች ተገቢውንክምና እንዲከታተሉ መደረጉንም ጠቅሰዋል

የቫይረሱን ከእናት ወደ ልጅ ስርጭት ለመግታትምሁሉም የጤና ተቋማት ጥምር የምርመራ ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራበት ይገኛል ብለዋል ኃላፊው።

የቲቢ  ምርመራ ከተደረገላቸው 12 ሺህ 201 ዜጎች  መካከል በሽታው የተገኘባቸው 3 ሺህ 789 ሰዎች መድሃኒት እንዲጀምሩ መደረጉም ተመላክቷል።

በሰለሞን ባረና

#ኢቢሲዶትስትሪም #ኢቲቪ #ኤችአይቪኤድስ #ቲቢ #ምርመራ #ሕክምና