Search

ባለፉት 45 ቀናት ብቻ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ክፍያ የፈፀመው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ቅዳሜ ነሐሴ 10, 2017 175

ከደንበኞቹ ዛሬ የቀረቡለትን የውጭ ምንዛሪ ማመልከቻዎች ሁሉንም በማጽደቅ 420.4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ዋጋ ያላቸውን የተለያዩ የውጭ ምንዛሪ ዓይነቶች ለተለያዩ ፍላጎቶች መፍቀዱን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ

ከሐምሌ 22 ቀን 2017 . ባንኩ 1 ሺህ 140 ደንበኞቹ በጥቅሉ የ541.4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ዋጋ ያላቸውን የተለያዩ የውጭ ምንዛሪ ዓይነቶች መፍቀዱን ባንኩ ለኢቢሲ ዶትስትሪም በላከው መረጃ ገልጿል

ይህም ከነዳጅ፣ ማዳበሪያ እና ሌሎች የአገልግሎት ክፍያዎች ጋር በተያያዘ በየቀኑ ከሚሰጠው መደበኛ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በተጨማሪ የተፈቀደ መሆኑን ነው የገለፀው።

እአአ ከጁላይ 1 ቀን 2025 ጀምሮ ለገቢ ንግድና ለአገልግሎት ክፍያ በአጠቃላይ 1.034 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ዋጋ ያለው የውጭ ምንዛሪ ክፍያ መፈፀሙን አክሎ ገልጿል።

በቀጣይም ከደንበኞች ፍላጎት እና ቅድሚያሚሰጣቸው ሀገራዊ ስትራቴጂያዊ ዘርፎች ጋር በማጣጣም ለውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በመደበኛነት ምላሽ መስጠቱን እንደሚቀጥልም አረጋግጧል።

#ኢቢሲዶትስትሪም #የኢትዮጵያንግድባንክ #የውጭምንዛሪ