Search

199ኛው የማንቹሪያን ደርቢ በማንቸስተር ሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

እሑድ መስከረም 03, 2019 108

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት በኦልድ ትራፎርድ ማንቸስተር ዩናይትድን የገጠመው ማንቸስተር ሲቲ 1 0 በማሸነፍ አራተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።

ፊል ፎደን ብሩኖ ፈርናንዴዝ ላይ ጥፋት ፈፅሟል ተብሎ በቀይ ካርድ ከሜዳ በተሰናበተበት ጨዋታ፣ የማንቸስተር ሲቲን ብቸኛ ግብ 60ኛው ደቂቃ ላይ ኤርሊንግ ሃላንድ አስቆጥሯል።

ውጤቱን ተከትሎ 12 ነጥብ የሰበሰበው ሲቲ በአርሰናል በግብ ክፍያ ተበልጦ 2 ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፣ ከአራቱ ጨዋታዎች 2 ጊዜ የተሸነፈው ማንቸስተር ዩናይትድ 13 ደረጃ ላይ ለመቀመጥ ተገዷል።

 

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: