Search

የ2019 የትምህርት ዘመን መማር ማስተማር ሥራ ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በይፋ ተጀመረ

ማክሰኞ መስከረም 05, 2019 121

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ በክልሉ 2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ መጀመሩን አስታውቋል።

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (/) በአዳማ ከተማ በሚገኘው ገዳ ኪሎሌ ትምህርት ቤት በመገኘት የመማር ማስተማር ሥራውን አስጀምረዋል።

ኃላፊው መምህራን ባላቸው ዕውቀት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲሰጡ፣ ወላጆች የልጆቻቸውን ትምህርት በቅርበት እንዲከታተሉ እንዲሁም ተማሪዎች ጥሩ ውጤት ለማምጣት ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲያጠኑ አሳስበዋል።

2019 የትምህርት ዘመን 13 ሚሊዮን 500 ሺህ ተማሪዎችን ለማስተማር ታቅዶ እስካሁን 7 ሚሊዮን ተማሪዎች መመዝገባቸውን / ቶላ ጠቁመዋል።

ከሚቀጥለው እሁድ በኋላ ምንም ዓይነት ምዝገባ እንደማይኖር አስታውሰው፣ ወላጆች ያልተመዘገቡ ልጆቻቸውን በፍጥነት በማስመዝገብ ትምህርት ማስጀመር እንዳለባቸው ጥሪ ማቅረባቸውን ኦቢኤን ዘግቧል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: