በአምስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አስቶን ቪላን በሜዳው ያስተናገደው ቶተንሃም 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።
ቶተንሃም በውድድር ዓመቱ ለሦስተኛ ጊዜ በተረታበት በዚህ ጨዋታ፣ የአስቶን ቪላን የማሸነፊያ ግቦች ዮሃን ማንዛምቢ፣ ኒኮላስ ጃክሰን እና ኤሚሊያኖ ቡንዲያ አስቆጥረዋል።
ቶተንሃምን ከሽንፈት ያልታደጉትን የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ግቦች ከመረብ ያሳረፉት ኮነር ጋላገር እና ቫን ሄክ ናቸው።
ቶተንሃም ካደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች ለሦስተኛ ጊዜ መሸነፉን ተከትሎ በሁለት ነጥብ የወራጅ ቀጠናው 18ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ፤ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን ያሳካው አስቶን ቪላ ደግሞ በአራት ነጥብ ደረጃውን ወደ 15ኛ አሻሽሏል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: