ፈረንሳዊው የባርሴሎና የተከላካይ መስመር ተሰላፊ ጁሌስ ኩንዴ በባርሴሎና ቤት ውሉን አራዝሟል።
ኩንዴ በስፔኑ ቡድን እስከ 2027 የሚቆይ ውል የነበረው ሲሆን አሁን ላይ እስከ 2030 የሚያቆየውን አዲስ ውል ተፈራርሟል።
ኩንዴ ከሲቪያ ባርሴሎናን ከተቀላቀለ በኋላ ከቡድኑ ወሳኝ ተጫዋቾች መካከል አንዱ መሆን ችሏል።
በባርሴሎና በ142 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ በመጫወት 5 ዋንጫዎችን ማሸነፍ ችሏል።
በሃብተሚካኤል ክፍሉ
#EBC #ebcdotstream #sports