Search

በአቶ አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ ፕሬዝዳንት ጋር ተወያየ

ሓሙስ ታኅሣሥ 09, 2018 34

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ ጋር ውይይት አድርጓል።

የልዑካን ቡድኑ ከፕሬዝዳንቱ ጋር በነበረው ቆይታ በቀጠናው ተምሳሌታዊ የሆነውን የሁለቱን ሀገራት ትስስር ይበልጥ በማጠናከር ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክሯል።

በተጨማሪም ሁለቱ ሀገራት በጋራ የሚያስተዳድሯቸው ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን ገምግሟል።

የልዑካን ቡድኑ በተጨማሪም የዶራሌ ሁለገብ ወደብን የጎበኘ ሲሆን፣ ወደቡ ለኢትዮጵያ ወጪ እና ገቢ ምርቶች እየሰጠ ያለውን አገልግሎት እንዲሁም ከወደቡ በባቡር ከባድ ጭነትን ወደ ሀገር ቤት የማጓጓዝ እንቅስቃሴ ያለበትን ሁኔታ ተመልክቷል።

የልዑካን ቡድኑ ተልዕኮውን አጠናቆ ማምሻውን ወደ ሀገር ቤት መመለሱን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።

#Ebc #Ebcdotstream #Ethiopia #Djibouti