የባህር ዳር ስታዲየም በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ጊዜያዊ ፍቃድ ማግኘቱን ተከትሎ፤ መስከረም ወር ላይ የሚያደርገውን የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን በሀገሩ ማድረግ እንደሚያስችለው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በቅርቡ በባህር ዳር ስታዲየም ላይ ያደረገውን ፍተሻ እና ግምገማ ተከተሎ ብሔራዊ ቡድናችን በመስከረም ወር 2019 በሜዳው ለሚያደርገው ጨዋታ የሚያገለግል ጊዜያዊ የካቴጎሪ 3 (CAT 3) ፈቃድ መስጠቱን ነው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በላከው ደብዳቤ ያሳወቀው።
ካፍ በስታዲየሙ የተመዘገቡ መሻሻሎችን በማድነቅ በላከው ደብዳቤ አሁንም ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ያልተጠናቀቁ ጉዳዮች እንዳሉ ገልጿል። የተቆጣጣሪ ቡድኑን ግኝቶች እና የሚቀሩ የማስተካከያ እርምጃዎችን የያዘ ሙሉ ቴክኒካዊ ሪፖርት በቅርቡ ለፌዴሬሽኑ እንደሚላክም ገልጿል።
ጨዋታው በሚደረግበት ቀን የስታዲየሙን ዝግጁነት እና የደንቦች አተገባበር ለመከታተል የስታዲየም ተቆጣጣሪ ሊመድብ እንደሚችልም ካፍ አስታውቋል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: