Search

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን በሀገሩ ያደርጋል

እሑድ ነሐሴ 10, 2018 58

የባህር ዳር ስታዲየም በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ጊዜያዊ ፍቃድ ማግኘቱን ተከትሎ፤ መስከረም ወር ላይ የሚያደርገውን 2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን በሀገሩ ማድረግ እንደሚያስችለው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በቅርቡ በባህር ዳር ስታዲየም ላይ ያደረገውን ፍተሻ እና ግምገማ ተከተሎ ብሔራዊ ቡድናችን በመስከረም ወር 2019 በሜዳው ለሚያደርገው ጨዋታ የሚያገለግል ጊዜያዊ የካቴጎሪ 3 (CAT 3) ፈቃድ መስጠቱን ነው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በላከው ደብዳቤ ያሳወቀው።

ካፍ በስታዲየሙ የተመዘገቡ መሻሻሎችን በማድነቅ በላከው ደብዳቤ አሁንም ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ያልተጠናቀቁ ጉዳዮች እንዳሉ ገልጿል። የተቆጣጣሪ ቡድኑን ግኝቶች እና የሚቀሩ የማስተካከያ እርምጃዎችን የያዘ ሙሉ ቴክኒካዊ ሪፖርት በቅርቡ ለፌዴሬሽኑ እንደሚላክም ገልጿል።

ጨዋታው በሚደረግበት ቀን የስታዲየሙን ዝግጁነት እና የደንቦች አተገባበር ለመከታተል የስታዲየም ተቆጣጣሪ ሊመድብ እንደሚችልም ካፍ አስታውቋል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: