Search

የማንችስተር ደርቢ በሲቲ 3 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቀቀ

እሑድ መስከረም 04, 2018 26

ለ197ኛ ጊዜ የተደረገው የማንቹሪያን ደርቢ በማንችስተር ሲቲ አሸናፊነት ሲጠናቀቅ ኧርሊንግ ብሮውት ሃላንድ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
በኢትሀድ በተደረገው የ4ኛ ሳምንት ጨዋታ ፊል ፎደን ደግሞ አንዷን ግብ ያስቆጠረ ተጫዋች ሆኗል፡፡
ሃላንድ ዩናይትድ ላይ 8ኛ ግቡን ሲያቆጥር ፊል ፎደን 7ኛ የደርቢ ግቡን ከመረብ አሳርፏል፡፡
ማንችስተር ሲቲ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰበትን ውጤት አስመዝግቧል፡፡
የፔፕ ጋርዲዮላ ስብስብ በ5ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ከአርሰናል የሚገናኝም ይሆናል፡፡
በውጤት ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ማንችስተር ዩናይትድ ደግሞ ከቼልሲ ይጫወታል፡፡
 
በአንተነህ ሲሳይ