Search

10 ሚሊዮን ብር የተሸለመው ከ17 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ማክሰኞ ኅዳር 23, 2018 159

የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማት አበርክቷል።

ብሔራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ተከትሎ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ለብሔራዊ ቡድኑ የእራት ግብዣ አድርጓል።

ወ/ሮ ሸዊት በዚሁ ወቅት፥ ቡድኑ የመንግሥት እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጠንካራ ሥራ ውጤት መሆኑን ተናግረው፤ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎውም ጥሩ ውጤት ይዞ እንደሚመለስ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራ እና በባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

#ebc #ebcdotstream #ethiopia #nationalteam #U17