የመጀመሪያው የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሀሰን ዓሊ ከ27 ዓመታት የውጭ ቆይታ በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
አቶ ሀሰን አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ “አቶ ሀሰን ዓሊ ወደ ሦስት አሥርተ ዓመታት ከሚደርስ ጊዜ በኋላ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱ የተቀበልኳቸው በታላቅ ክብር ነው” ብለዋል።
የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሀሰን ዓሊ የክልሉ መንግሥት ዛሬ ለደረሰበት ደረጃ በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ ግለሰቦች መካከል አንዱ እንደሆኑም ጠቅሰዋል።
በሁሉም ደረጃዎች ለተወጡት ኃላፊነት እንዲሁም ለአገልግሎታቸው በራሳቸው እና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ስም አመስግነዋል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት በተለያዩ ምክንያቶች ከሕዝባቸው ርቀው የቆዩ የሕዝብ ልጆችን በጥንቱ እሴት መሠረት ወደ ቀዬአቸው ለማቅረብ ፍላጎት እና ቁርጠኝነቱ ያለው መሆኑን አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዚሁ አጋጣሚ አረጋግጠዋል።
አቶ ሀሰን ዓሊ ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1987 ዓ.ም ድረስ የመጀመሪያው የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ሆነው አገልግለዋል።
#ebcdotstream #EBC #Ethiopia