Search

አፍሪካ እና ቻይና የ2026 የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ፕሮግራምን ይፋ አደረጉ

ሓሙስ ታኅሣሥ 30, 2018 75

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን እና ቻይና የ2026 የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት የጋራ ፕሮግራምን ዛሬ በአዲስ አበባ ይፋ አደረጉ።
ፕሮግራሙ ይፋ ሲደረግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አፅቀሥላሴ፣ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ፣ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በቻይና እና አፍሪካ መካከል ያለውን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እንደሚያሳድግ ለታመነበት ፕሮግራም የራሱ መለያ (ሎጎ ) ይፋ ሆኗል።
 
በሞላ ዓለማየሁ