Search

ኢትዮጵያ ግዙፉን ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ኮንፈረንስ (WIC) ልታስተናግድ ነው!

ረቡዕ ጥር 13, 2018 245

ኢትዮጵያ ከቻይና ውጭ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ግዙፉን ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ኮንፈረንስ (World Internet Conference - WIC) በመጪው መስከረም ወር በአዲስ አበባ ለማስተናገድ ዝግጅቷን እያጠናቀቀች መሆኑ ተገልጿል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (/) WIC ምክትል ዋና ፀሐፊ ሚስተር ሊያን ሃኦን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ምክክሩ በዋናነት ኮንፈረንሱ በስኬት እንዲከናወን በሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ላይ ያተኮረ እንደነበር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።

🔥 ኮንፈረንሱ ለኢትዮጵያ ያለው ፋይዳ

ይህ ኮንፈረንስ ለሀገራችን በርካታ ጥቅሞችን ይዞ እንደሚመጣ ይጠበቃል፦

የቴክኖሎጂ ሽግግር፡ እንደ Google NVIDIA IBM እና Alibaba ያሉ 200 በላይ ዓለም ግዙፍ የቴክኖሎጂ ተቋማት የሚሳተፉበት በመሆኑ ለኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ዕድገት ትልቅ አቅም ይፈጥራል።

ኮንፈረንስ ቱሪዝም፡ አዲስ አበባን የዓለም አቀፍ ስብሰባዎች መዳረሻ (Hub) የማድረግ ራዕይን ያሳካል።

ኢንቨስትመንት፡ የዓለም አቀፍ የዘርፉ ተዋናዮችና ምሁራን በሚሳተፉበት በዚህ መድረክ አዳዲስ የኢንቨስትመንት በሮች ይከፈታሉ።

👉 ስለ ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ኮንፈረንስ (WIC) በጥቂቱ

2012 ጀምሮ በየዓመቱ በቻይና ሲካሄድ የቆየው ይህ ታዋቂ ኮንፈረንስ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቻይና ውጭ እንዲካሄድ ሲወሰን ኢትዮጵያ መመረጧ የሀገራችንን ዲፕሎማሲያዊ ተቀባይነትና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያመጣችውን እመርታ የሚያሳይ ነው።

/ በለጠ ሞላ፥ ኢትዮጵያ እንዲህ ያሉ ታላላቅ ሁነቶችን የማስተናገድ በቂ ልምድ ያላት በመሆኑ፣ ኮንፈረንሱን በላቀ ደረጃ ለማስተናገድ አስፈላጊው ዝግጅት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

#EBC #EBCDOTSTREAM #WIC #InternetConference #Ethiopia #Technology #Innovation #AddisAbaba