Search

ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ አልሚዎች የመሥሪያ ቦታ በምደባ እንዲሰጥ የሐረሪ ክልል ካቢኔ ውሳኔ አስተላለፈ

ሓሙስ ጥር 21, 2018 123

የሐረሪ ክልል መስተዳደር ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ አልሚዎች በክልሉ እንዲያለሙ የመሥሪያ ቦታ በምደባ እንዲሰጥ ውሳኔ አስተላልፏል።

የመሥሪያ ቦታ እንዲሰጥ ውሳኔ የተላለፈውም ልዩ ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው በተለይ በሆቴል እና ቱሪዝም፣ በአግሮ ኢንዱስትሪ እና ማኑፋክቸሪንግ፣ በቅይጥ አገልግሎት እና በጋራ የመኖሪያ ቤት አፓርትመንት እንዲሁም በመዝናኛ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ነው።

መስተዳድር ምክር ቤቱ በአጀንዳው ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።

የክልሉ መንግሥት የኢንቨስትመንት ዘርፉን የበለጠ ለማነቃቃት በትኩረት እየሠራ መሆኑ ተመላክቷል።

በቀጣይም ፋይዳ ባላቸው እና የሕዝብን ተጠቃሚነት በሚያጎለብቱ ዘርፎች ላይ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።

#EBC #EBCDotstream #Ethiopia #Harari