የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞውን እያፋጠነ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልእክት፤ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኘው የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ 10 የተለያዩ ተቋማትን በአንድ ጥላ ስር በማስተናገድ 73 የሚደርሱ አገልግሎቶችን ለዜጎች በተቀላጠፈ መልኩ በመስጠት ላይ ይገኛል ብለዋል።
ማዕከሉ ተገልጋዮችን በዘመናዊ መንገድ ለማስተናገድ እንዲያስችለው 96 ካውንተሮች እንዲኖሩት ተደርጎ መደራጀቱን ገልጸው፤ ስራ በጀመረባቸው በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ ብቻ ከ23 ሺህ በላይ ተገልጋዮችን ተቀብሎ በማስተናገድ ውጤታማነቱን በተግባር ማሳየቱን ጠቅሰዋል።
ይህ ተቋም አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማዘመን የጀመረውን የተቀላጠፈ የዲጂታል አሰራር በስፋት ተግባራዊ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝም አመልክተዋል።
#ድሬዳዋ #ድሬመሶብ #የአንድማዕከልአገልግሎት #ዲጂታልኢትዮጵያ #DireDawa #OneStopService #DigitalTransformation #Ethiopia