Search

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጋሞ ዞን በደረሰው አደጋ የተጎዱ ወገኖችን በስፍራው በመገኘት አጽናኑ

ቅዳሜ መጋቢት 05, 2018 60

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ወገኖችን በስፍራው በመገኘት አጽናንተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በበልግ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸው ላለፈ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ገልጸዋል።
መንግሥት ለአደጋው ተጎጂዎች አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲቻል ተገቢው ጥናትና ሥራ መከናወን እንዳለበት ያሳሰቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰትም አስፈላጊው የጥንቃቄ ተግባራት ሊከናወኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።