Search

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የአማራ ክልል ሕዝብ እና አመራሩ ወደ አዲስ የመንቃት ምዕራፍ የተሻገሩበት የልዩ ዘመን መክፈቻ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ቅዳሜ ግንቦት 29, 2018 60

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ የከፍተኛ አመራሮች የግምገማ መድረክ መካሄዱን እና በመድረኩ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም እና ስትራቴጂካዊ ውጤቶች በጥልቀት መገምገሙን ገልጸዋል።

ይህ ምርጫ የክልሉ ሕዝብ እና አመራር ከጠላት መጠነ ሰፊ ሴራዎች ከፍ ብለው በመራመድ፣ ለክልሉ ዘላቂ ልማት እና ሰላም በጠራ መስመር እና በማይናወጥ አንድነት በመቆም የማይሻር ገድል የፈጸሙበት ነው ብለዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ሕዝባችን በዚህ ምርጫ ያሳየው ወደር የለሽ የሰላም ቁርጠኝነት እና የዴሞክራሲ ብስለት፤ በክልሉ ላይ በባዕዳን እና በባንዳዎች የተጋረጡ የጥፋት ማነቆዎችን ሙሉ በሙሉ እንዲቀለበሱ አስችሏል ሲሉ ገልጸዋል።

በቀጣይም የክልሉን እምቅ አቅም ለመጠቀም ሰላምን በዘላቂነት ማጽናት፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን እና የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች በቁርጠኝነት መመለስ ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ በግምገማው የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን አረጋግጠዋል።