Search

የበጀት ጉድለቱ በ7 ዓመታት ውስጥ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ደርሷል - የገንዘብ ሚኒስቴር

ሓሙስ ሰኔ 04, 2018 79

በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የኢትዮጵያ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያለው ድርሻ 2018 በጀት ዓመት ወደ 9.5 በመቶ ከፍ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ አስታወቁ።

ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5 ዓመት የሥራ ዘመን 25 መደበኛ ስብሰባ ላይ 2019 በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድን ለውይይት ባቀረቡበት ወቅት ነው።

አቶ አሕመድ ሽዴ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፣ የግብር አሰባሰብን ለማሳለጥ እና የታክስ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የወጣው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን ስትራቴጂ ውጤት እያስገኘ ነው።

በዚህም መሠረት ከበርካታ ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ 2017 በጀት ዓመት ሀገራዊ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጋር ያለው ጥምርታ 1.6 በመቶ በመጨመር፣ 2016 ከነበረበት 6.2 በመቶ ወደ 7.7 በመቶ ከፍ ማለቱን አብራርተዋል።

ይህ አፈጻጸም 2018 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ በመቀጠሉ ድርሻው ወደ 9.5 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚገመት አመልክተዋል።

ለዚህ ስኬት የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የኤክሳይዝ ታክስ እና የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያዎች እንዲሁም የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሥርዓት ማሻሻያ መደረጉ በዋናነት ይጠቀሳሉ።

ሚኒስትሩ አክለውም ከዚህ ቀደም በጥቅሉ ሲሰጡ የነበሩ እና ተገቢውን ውጤት የማያመጡ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን በመቀነስ፣ ማበረታቻው ኢንቨስተሮች በሀገር ውስጥ ከሚያስመዘግቡት የሥራ ዕድል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የካፒታል ፈጠራ ጋር በቀጥታ እንዲገናኝ መደረጉ ሀገራችን ታጣው የነበረውን ከፍተኛ ገቢ ለማስቀረት ማስቻሉን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የመንግሥት የፊስካል ጉድለት መጠን ከፍተኛ መሻሻል ማሳየቱን የጠቀሱት አቶ አሕመድ 2017 በጀት ዓመት 7 ዓመታት ውስጥ ዝቅተኛው የበጀት ጉድለት መመዝገቡን ይፋ አድርገዋል።

ይህም ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርት (GDP) አኳያ አንድ በመቶ ብቻ መሆኑን እና 2014 . ከነበረበት 4.1 በመቶ አንጻር ሲታይ እጅግ ከፍተኛ መሻሻል መሆኑን አስረድተዋል።

በበረከት ሽመልስ