Search

ያልተቋረጠው የሊዮኔል ሜሲ ስኬት

ረቡዕ ሰኔ 10, 2018 78

እያደሩ መጣፈጥ ለእርሱ የተፈጠረ ይመስላል። የትናንቱ ጨዋታ ውጤት የመጨረሻው መጀመሪያ ምልክት እንጂ፤ የድል መጀመሪያ አይደለም፤ ፍጻሜም አይመስልም።

የሮዛሪዮ ሳንታፌው ልጅ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ፣ 23 ዓመታት በፊት 20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አንስቶ አርጀንቲናን ወክሏል።

ይህ ከመሆኑ በፊት በስፔን ካታሎኒያ የሚገኙት የሜሲ ዘመዶች፣ ገና በአፍላ ዕድሜው በትውልድ ቀዬው ሮዛሪዮ ያሳየውን የእግር ኳስ ተሰጥኦ ተመልክተው ዕድል በማመቻቸታቸው፤ ወደ ግዙፉ የባርሴሎና ክለብ የሚያደርሰውን የላማሲያ ታዳጊዎች ማሰልጠኛን ሊቀላቀል ችሏል።

ከዚህ በኋላ 'ድንቁ ባለ ግራ እግር ተጫዋች በእግር ኳሱ ዓለም ምን አደረገ?' የሚል ጥያቄ ከተነሳ፤ መልሱየቀረው ታሪክን ነውየሚል ይሆናል።

አሁን ደግሞ ወደአልቢሴሌስቴዎቹመንደር፣ ወደነ ዲዬጎ አርማንዶ ማራዶና ቅጽር እንዝለቅ።

 

 

ሜሲ በግራ እግሩ የዓለምን እግር ኳስ ወደ ሌላ ምዕራፍ ሲያሻግር የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ግን ለዚህ ስኬት ሳይታደል ቆይቷል።

በካታሎኒያ እንደተደጋገሙት ሜሲን የተንተራሱ ድሎች፤ ቦነስ አይረስ ሳትቋደሳቸው ረጅም ዓመታት ነጎዱ።

ቡድኑን ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ያበቃ ውጤት ቢያስመዘግብም፣ ከዋንጫው ጋር ግን ተራራቀ። በዚህም አርጀንቲናውያን ክፉኛ አዘኑ።

ሜሲ እነዚህ ጫናዎች ሲከብዱት እና በውኃ ሰማያዊው መለያ ልክ እንደ ካምፕ ኑው ውጤት አልሰምር ሲለው፤ 'ቢበቃኝስ' እስከማለት ደረሰ።

ውሳኔውን ተከትሎም የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድንን መለያ ዳግም እንደማይለብስ አስታወቀ። ይህ በወቅቱ እጅግ አስደንጋጭ ዜና ነበር።

2016 የኮፓ አሜሪካ ሽንፈት በኋላ የመጣው ይህ የሜሲ ውሳኔ እንዲቀለበስ፤ የወቅቱ የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ማውሪሲዮ ማክሪ እና ኮከቡ ዲዬጎ ማራዶና ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ሜሲ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ተመለሰ።

የተመለሰበት ዋና ዓላማ ደግሞ፣ ከእጆቹ ያመለጠውን የኮፓ አሜሪካ እና ትልቁን የዓለም ዋንጫ ለአልቢሴሌስቴዎቹ ማምጣት ነበር።

ይህንኑ ጥያቄ 2021 ኮፓ አሜሪካን፣ 2022 ደግሞ የዓለም ዋንጫን በማንሳት በተግባር መለሰ።

ያኔ ሜሲ ከዚህ በኋላ እግር ኳስን ቢሰናበት እንኳን፣ የስኬት መንገዱ ወደ ምሉዕነት ተጠግቷል የሚለው ሀሳብ ብዙዎችን አስማምቶ ነበር።

እርሱ ግን 'በቃኝ' ማለትን አልወደደም። በግልም ሆነ በቡድን፣ በክለብም ሆነ በብሔራዊ ቡድን፤ በድል ላይ ድል፣ በክብረ ወሰን ላይ ሌላ ክብረ ወሰን እየደራረበ መጓዙን ቀጥሏል።

2024 የኮፓ አሜሪካ ውድድር ላይም ተከታታይ ስኬቱን አስመዝግቦ፣ በአሜሪካ ምድር ወደሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞውን ቀጥሏል።

ሌሊቱን አርጀንቲና ካንሳስ ላይ አልጄሪያን ገጥማ 3 0 ስታሸንፍ፤ አሁንም ቡድኑ በሜሲ ትከሻ ላይ እንዳለ ባሳበቀ ሁኔታ ሦስቱንም ግቦች ያስቆጠረው እርሱ ነው።

ይህም በብሔራዊ ቡድን መለያ 11 ሀትሪኩ ሆኖ ተመዝግቧል። በዓለም ዋንጫ ታሪክም ሀትሪክ የሰራ አንጋፋው ተጫዋች ለመሆን በቅቷል።

የዓለም ዋንጫ አዳዲስ ኮከቦችን እንደሚያስመለክተው ሁሉ፤ እንደ ሜሲ ያሉትን የዘመን ክስተቶችም ማንገሱን ቀጥሏል። በእርግጥ 23 ዓመታት በእግር ኳስ ውስጥ እጅግ ብዙ ናቸው።

በእነዚህ ሁሉ ዓመታት የስኬት ምሳሌ እየተደረጉ መቀጠል ደግሞ እንደ ሜሲ ላሉ ጥቂት ተሰጥኦዎች እንጂ ለብዙዎች የሚቻል አይደለም።

'21ኛው ክፍለ ዘመን እግር ኳስ እርሱ ባይኖረው ምን ሊመስል ይችላል?' የሚል ጥያቄ ሲነሳ፤ታሪኩ አሁን ካለው የተለየ መልክ ይኖረው ነበርየሚል መልስ መከተሉ አይቀርም።

በሕይወት እስካለሁ፣ ጉልበቴ እስካልዛለ፣ ጤናዬም እስካልተጓደለ ድረስ ለምወዳት እግር ኳስ ያለኝን ሁሉ እሰጣለሁይህ ቃል፤ ከጨዋታው በኋላ የሰነዘረው ቁልፍ ሀሳብ ነው።

ሊዮኔል ሜሲ የመጀመሪያ የዓለም ዋንጫ ግቡን ባስቆጠረበት 2006 ውድድር እና በትናንቱ ሀትሪኩ መሀል 20 ዓመታት ልዩነት አለ።

አሁን ላይ በዓለም ዋንጫ መድረክ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን በዕድሜ ትንሹም ሆነ አንጋፋው ግብ አስቆጣሪ መሆን የቻለው እርሱ ነው።

በእድሪስ አህመድ