Search

ከ55 ኮርሶች 46ቱን 'A+' ያስመዘገበው ባለ ብሩህ አእምሮው መሐንዲስ

ሓሙስ ሰኔ 18, 2018 49

 

አላምረው ዋጋው በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ትምህርት ክፍል 2018 ትምህርት ዘመን እጩ ተመራቂ ነው፡፡

አላምረው በዩኒቨርሲቲ ቆይታው 4 ነጥብ (CGPA) በማስመዝገብ የዩኒቨርሲቲው ልዩ ዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

ይህ ባለ ብሩህ አእምሮ ወጣት ዕጩ ተመራቂ መሐንዲስ ለዚህ ከፍተኛ ክብር ሊበቃ የቻለው በትምህርት ቆይታው ከወሰዳቸው 55 አጠቃላይ ኮርሶች መካከል 46ቱን 'A+' እንዲሁም በቀሪዎቹ 9 ኮርሶች 'A' በማምጣት ባስመዘገበው ውጤት ነው።

አላምረው ዋጋው ባሳየው በዚህ አስደናቂ የትምህርት አፈጻጸም፣ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 7ኛው ዙር የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በልዩ ሁኔታ የዋንጫ ተሸላሚ መሆኑን ከአዊ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።