Search

ከ6 ሺህ ሄክታር ተነስቶ 1.5 ሚሊዮን ሄክታር የደረሰው የኦሮሚያ የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ

እሑድ ጥቅምት 02, 2018 204

በኦሮሚያ ክልሉ 6 ሺህ ሄክታር በታች በሆነ መሬት ላይ የተጀመረው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ 2018 . 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መድረሱን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

በክልሉ በጅማ፣ በኢሉአባቦር፣ በቡኖ በደሌ እንደዚሁም በወለጋ የሩዝ ምርት በስፋት እየተመረተ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊ ጌቱ ገመቹ ገልጸዋል።

ቀደም ሲል ከውጭ ይገባ የነበረውን የሩዝ ምርት በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት ታስቦ ወደ ተግባር መገባቱንም አቶ ጌቱ አስታውሰዋል።

2017 . የምርት ዘመን በክልሉ በሩዝ ከተሸፈነው መሬት 52 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

ኢቲቪ ያነጋገራቸው የጅማ ዞን፣ ሸቤ ሶምቦ ወረዳ፣ ኪሼ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ጀማል እድሪስ እና አርሶ አደር አዲሱ ሙሳ፥ የሩዝ ሰብል ከዚህ ቀደም ከሚዘሩዋቸው የተለያዩ አዝርዕት በተሻለ መልኩ ውጤታማ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።

ከዘንድሮው የምርት ዘመን የተሻለ  የሩዝ ምርት እናገኛለን ብለው እንደሚጠብቁም ተናግረዋል።

በዘንድሮው ዓመት ከሚያገኙት ምርት በመነሳትም በቀጣይ በሰፊ ማሳ ላይ ሩዝ የማምረት ሀሳብ እንዳላቸው ጠቁመዋል።

በወረዳው ቀድሞ ከሚታወቁ የሩዝ ዝርያዎች በተጨማሪ 14 አዳዲስ የሩዝ ዝርያዎች ቀርበው ስድስቱ በስራ ላይ መዋላቸውን የሸቤ ሶምቦ ወረዳ ግብርና ባለሙያዎች ለኢቲቪ ገልጸዋል።

በራሔል አብደላ

#ebcdotstream #etv #oromia #rice