Search

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የኢኮኖሚ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

ሰኞ ሚያዝያ 12, 2018 53

በገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ የተመራው ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን፣ ከ2026 የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የፀደይ ስብሰባ ጎን ለጎን ከአሜሪካ የግምጃ ቤት ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር የሚያስችል ውይይት አድርጓል።
ውይይቱ የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትሥሥርን በማሳደግ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ በተለይም እንደ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ልማት ባሉ ስልታዊ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ዙሪያ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለውን የሪፎርም ጉዞን አድንቀዋል።
የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር በቴክኒክ ድጋፍ፣ በግል ዘርፍ ተሳትፎ እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነትም በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ሁለቱም ወገኖች የጋራ የኢኮኖሚ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ወደፊት ለማራመድ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማፋጠን እና የሁለቱን ሀገራት የንግድ ትሥሥር ይበልጥ ለማስፋፋት ተስማምተዋል።