እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ተጠናክሮ መቀጠሉን እና አበረታች ደረጃ ላይ መድረሱን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታውቀዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ የምክክር ጉባኤውን ሂደት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት፣ በአሁኑ ወቅት 250ዎቹ የምክክር ቡድኖች አጀንዳዎቻቸውን ሁለት ጊዜ በመመልከት እና በማጠናቀር ለ500ዎቹ ቡድኖች እያዘጋጁ ይገኛሉ።
አብዛኛዎቹ ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን፣ አጠቃላይ የ250ዎቹ ቡድኖች የሀሳብ ማጠናቀር ሥራ ዛሬ ማታ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ቀጣዩ ሂደት ደግሞ 500ዎቹ ቡድኖች እነዚህን የተሰባሰቡ ሀሳቦች ይበልጥ በማዳበር ለዋናው ጉባኤ የሚያዘጋጁበት እንደሚሆን ፕሮፌሰር መስፍን ጠቁመዋል።
ይህ የሀሳብ ማጠናቀር እና የምክክር ሂደት ቀላል የሚባል እንዳልነበር ያስታወሱት ፕሮፌሰር መስፍን፣ ከ10 ቡድን ጀምሮ በርካታ የሀሳብ ፍጭቶች ሲደረጉባቸው መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በመጀመሪያዎቹ ምዕራፎች ላይ ተሳታፊዎች ያመጡት ሀሳብ እንደመጣ እንዲያልፍላቸው ይፈልጉ ስለነበር ከፍተኛ መጨቃጨቆች እና መጎራበጦች ታይተው እንደነበር አልሸሸጉም።
ይሁን እንጂ ኮሚሽኑ ውይይቶቹ በግለሰቦች ላይ ሳይሆን በሀሳብ ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ በቅርበት እየተከታተለ እና እየተቆጣጠረ እዚህ በመድረሱ፣ በአሁኑ ወቅት ውይይቱ እየለዘበ መጥቶ ትክክለኛውን የመግባባት መሥመር ሊይዝ መቻሉን ዋና ኮሚሽነሩ አረጋግጠዋል።
በለሚ ታደሰ
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: